አቡነ ዜና ማርቆስ የአረጋውያንና የሕጻናት መርጃ ማኅበር

ሁላችንም የዜግነት ሓላፊነታችንን ለመወጣት ብንተጋ በሌሎች ሰዎች ሕይወት ውስጥ ለውጥ ማምጣት  እንችላለን!

ነገን ዛሬ ላይ  እንገንባ!

ስያሜ

 

አቡነ ዜና ማርቆስ በ 12ኛ መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ናቸው።

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፈሎች እየተዘዋወሩ ሥራን፣ ፍቅርን፣ መረዳዳትንና  በሥርዓት መኖርን በማስተማር በተጨማሪም ብሔር፣  ሃይማኖትና ወገን ሳይለዩ ለተቸገረ በመርዳት በማኅበረሰቡ ውስጥ ፍቅርን በማሳየት አርአያ ሆነዋል። 

ዕቁብ የተባለውን ባሕላዊ የገንዘብ ቁጠባ ዘዴን በመጀመርና በማስፋፋት  ወገን ከወገኑ ጋር እንዴት ማደግ እንደሚችል አሳይተዋል። ለሀገርና ለወገን መልካም ያደረጉትን ለማዘከርና  አርኣያነታቸውን ለመከተል በማሰብ  የዚህ ማኅበር ስያሜ አቡነ ዜና ማርቆስ  ተብሏል።

ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ ግብ እና ዓላማ

 

ራዕይ

 

ለችግር የተጋለጡ ህጻናትና አረጋውያን ሁለንተናዊ አቅማቸው ጎልብቶ ለማኅበረሰቡ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሲያበረክቱ ማየት

 

 

ተልዕኮ

ወገን ለወገኑ የሚደርስበትን ባህል በማዳበር ከቤተሰቦች፣ ከማኅበረሰቡና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለችግር የተጋለጡ ህጻናትና አረጋውያን ሙሉ ድጋፍ አግኝተው ሁለንተናዊ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ማስቻል

ግብ

  • ለችግር የተጋለጡ ህጻናት በትምህርትና በሥነ-ምግባር የታነጹ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ማስቻል እና ወላጆቻቸውን ከጠባቂነት በማላቀቅ ወደ ሥራ ማስገባት
  • ጧሪና ቀባሪ ያጡ አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን መርዳትና መንከባከብ

ዓላማ

  • ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ህፃናት የምግብ፣ የአልባሳት፣ የትምህርትና  የምክር  እርዳታ እንዲያገኙ፣ ወላጆቻቸውንም ከችግር ለማውጣት  የሥራ  ተነሳሽነትን  በመፍጠር ወደ  ሥራ  እንዲገቡና  ልጆቻቸውን እንዲያሳድጉ ማስቻል
  • ረዳት  ያጡ  አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን የሞራል፣  የምግብ፣ የአልባሳትና  የሕክምና  እርዳታ  እንዲያገኙ ማድረግ

የማኅበሩ  ዋና ዋና የሥራ ክፍሎች

  1. መስራት የሚችሉ ወገኖችን መስራት እንዲችሉ የማድረግ ፕሮጀክት

  2. ጧሪ ቀባሪ ያጡ አረጋውያንንና አቅመ ደካሞችን መንከባከብ

  3. መማር እየፈለጉ መማር ያልቻሉ ሕጻናትን እንዲማሩ ማድረግ